እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

እንኳን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ድረ ገጽ በደህና መጡ!

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ መንግስታዊ የሆነ ተቋም ነው።

የቅርብ ጊዜ ዜናችን

የቅርብ ጊዜ ዜናዎችን እና ክስተቶችን ያንብቡ

የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ ተጠቆመ።

በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ የተጀመረውን የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ጠቁመዋል።
ትምህርት የሁሉም መሠረት እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትር ደኤታዋ በትምህርት ስርዓቱ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን መሠረት ለመጣል ጠንክሮ መሥራት ይገባል ብለዋል።
በዚህም የትምህርት ስብራቱን ለማከም የሚያስችል አሻራ መጣልና ለውጥ ማምጣት እንደሚያስፈልግም ገልፀው አሁን በትምህርት ዘርፉ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተጀመሩ ሥራዎችን የበለጠ ለማላቅ በበለጠ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት አመራሮቹ እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በትምህርት ለትውልድ መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አሰተዳደሮች ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገለጿል።
በትምህርት ዘርፉ የተካሄደው የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ህብረተሰቡ በትምህርት ላይ ያለውን የባለቤትነት ሚና በትክክል ያረጋገጠና ለሌሎች ሴክተሮችም ተሞክሮ መሆን እንደሚችል በመድረኩ ተነስቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን በክልሎች ያደረገው ምልከታ ሪፖርትም በመድረኩ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የሱፐርቪዥኑ ዓላማ መደጋገፍ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በሱፐርቪዥኑ የታዩ መልካም አፈፃፀሞችን ማጠናከር እንዲሁም የታዩ ክፍተቶችን ደግሞ በቀጣይ በዕቅድ አካቶ ለመስራት እድል የሚፈጥር ነውም ተብሏል።
በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገልጿል።
ባለፈው ዓመት መጨረሻ ላይ የተጀመረውን የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ ማስቀጠል እንደሚገባ አጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ ጠቁመዋል።
ትምህርት የሁሉም መሠረት እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትር ደኤታዋ በትምህርት ስርዓቱ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን መሠረት ለመጣል ጠንክሮ መሥራት ይገባል ብለዋል።
በዚህም የትምህርት ስብራቱን ለማከም የሚያስችል አሻራ መጣልና ለውጥ ማምጣት እንደሚያስፈልግም ገልፀው አሁን በትምህርት ዘርፉ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተጀመሩ ሥራዎችን የበለጠ ለማላቅ በበለጠ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት አመራሮቹ እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በትምህርት ለትውልድ መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አሰተዳደሮች ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ማሰባሰብ መቻሉም ተገለጿል።
በትምህርት ዘርፉ የተካሄደው የትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ ህብረተሰቡ በትምህርት ላይ ያለውን የባለቤትነት ሚና በትክክል ያረጋገጠና ለሌሎች ሴክተሮችም ተሞክሮ መሆን እንደሚችል በመድረኩ ተነስቷል።
የትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን በክልሎች ያደረገው ምልከታ ሪፖርትም በመድረኩ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የሱፐርቪዥኑ ዓላማ መደጋገፍ የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በሱፐርቪዥኑ የታዩ መልካም አፈፃፀሞችን ማጠናከር እንዲሁም የታዩ ክፍተቶችን ደግሞ በቀጣይ በዕቅድ አካቶ ለመስራት እድል የሚፈጥር ነውም ተብሏል።
Apr 29, 2024 198
የሀገር ውስጥ ዜና

በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች በክረምት ስልጠና እንደሚሠጣቸው ተገለፀ።

በዚህ ዓመት በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመምህራን የክረምት ስልጠና ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ይሠጣል ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ይህ የሚሠጠው የክረምት ስልጠና አሁን እያስተማሩ ያሉ መምህራን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ ክህሎት እንዲይዙ ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም መምህራን በሚያገኙት ስልጠና በሚያስተምሩት ትምህርት ላይ ትምህርቱን በበቂ ማስተማር የሚያስችላቸው ክህሎት ያገኛሉም ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የመምህራንና ትምህርት አመራሮች የክረምት ስልጠና የተሳካ እንዲሆን ክልሎች ተባብረው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመምህራን የክረምት ስልጠና አተገባበር ስትራቴጂ በመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱም የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ለመምህራን የሚሰጠው ስልጠና መምህራኑ በሚያስተምሩት ትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ በመሆኑ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ጠቃሚ መሆኑንም አንስተዋል
በዚህ ዓመት በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመምህራን የክረምት ስልጠና ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ይሠጣል ተብሏል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ይህ የሚሠጠው የክረምት ስልጠና አሁን እያስተማሩ ያሉ መምህራን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ ክህሎት እንዲይዙ ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም መምህራን በሚያገኙት ስልጠና በሚያስተምሩት ትምህርት ላይ ትምህርቱን በበቂ ማስተማር የሚያስችላቸው ክህሎት ያገኛሉም ብለዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ይህ የመምህራንና ትምህርት አመራሮች የክረምት ስልጠና የተሳካ እንዲሆን ክልሎች ተባብረው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመምህራን የክረምት ስልጠና አተገባበር ስትራቴጂ በመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱም የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ለመምህራን የሚሰጠው ስልጠና መምህራኑ በሚያስተምሩት ትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ በመሆኑ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ጠቃሚ መሆኑንም አንስተዋል
Apr 29, 2024 307
የሀገር ውስጥ ዜና

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል።
የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦን ላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ብለዋል።
ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኛች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦን ላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ምክክር መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል ።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በኦን ላይን ለመስጠት ባይቻልም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን ይወስዳሉም ብለዋል።
የሀገር አቀፍ ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ዶ/ር) እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፈተናውን በኦን ላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚለቀቅላቸው ሲሆን ደጋግመው እንዲሞክሩና እንዲለማመዱ ይደረጋልም ብለዋል።
ለዚህም እንዲረዳ የአሰልጣኛች ስልጠና በመሥጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሠጣቸውም ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት እንደሚጀምርም በመድረኩ ተገልጿል።
Apr 27, 2024 241
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ዘርፉ ውጤታማ ስራ ለመሥራት የተግባባ፣ የጋራ አስተሳሰብ ያለውና የወደፊቱን የተገናዘበ አመራር መስጠት እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለፁ።

የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የምክክር መድረክ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልል የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የተገኙት ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት የመምራት እድል እንደተሰጠው አመራር በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ያለውን ውስብስብ ችግር በመረዳት የተቀራረበ አመለካከት በመያዝ አመራር መስጠት ይገባል ብለዋል።
ከዚህ በፊት ትምህርትን እያየን ባለንበት መንገድ መሥራት አንችልም ያሉት ሚኒሰትሩ በረጅም ጊዜ አቅደን ብቁ ተወዳዳሪ እና በስነ-ምግባር የታነፁ ልጆች ለማፍራት የሚያስችል ትምህርት እየሰጠን ነው የሚለውን ማሰብና መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ዘርፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ የጋራ አስተሳሰብ በአዲስ መልክና ማዕቀፍ መያዝ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ከአጭር ጊዜ አስተሳሰብ ወጥተን የሚቀጥለውን ትውልድ በዓለም ተወዳዳሪ፣ ክህሎት ያለው፣ ግብረ ገብነትን የተላበሰ እንዲሆን ለማድረግ የጋራ አስተሳሰብ ይዞ መሄድ እንደሚገባም አሳስበዋል።
አሁን ዓለም ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት የተሻለ ብቃትና ክህሎት ያላቸው እንዲሁም በስነ ምግባር የታነፁ ተማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።
በመድረኩም የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ፣ የህዝብ ተወካዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣ የሁሉም ክልልና ሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የምክክር መድረክ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልል የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የተገኙት ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት የመምራት እድል እንደተሰጠው አመራር በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ያለውን ውስብስብ ችግር በመረዳት የተቀራረበ አመለካከት በመያዝ አመራር መስጠት ይገባል ብለዋል።
ከዚህ በፊት ትምህርትን እያየን ባለንበት መንገድ መሥራት አንችልም ያሉት ሚኒሰትሩ በረጅም ጊዜ አቅደን ብቁ ተወዳዳሪ እና በስነ-ምግባር የታነፁ ልጆች ለማፍራት የሚያስችል ትምህርት እየሰጠን ነው የሚለውን ማሰብና መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በትምህርት ዘርፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ የጋራ አስተሳሰብ በአዲስ መልክና ማዕቀፍ መያዝ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ከአጭር ጊዜ አስተሳሰብ ወጥተን የሚቀጥለውን ትውልድ በዓለም ተወዳዳሪ፣ ክህሎት ያለው፣ ግብረ ገብነትን የተላበሰ እንዲሆን ለማድረግ የጋራ አስተሳሰብ ይዞ መሄድ እንደሚገባም አሳስበዋል።
አሁን ዓለም ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት የተሻለ ብቃትና ክህሎት ያላቸው እንዲሁም በስነ ምግባር የታነፁ ተማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።
በመድረኩም የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ፣ የህዝብ ተወካዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣ የሁሉም ክልልና ሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
Apr 26, 2024 158
የሀገር ውስጥ ዜና

ሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ስኬታማነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተጠየቀ፡፡

በኦሮሚያ ብ/ክ/መ/በአርሲ ዞን የሌሙና ብልብሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጫላ አበራ የቢልቢሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የጎልማሶች መማሪያ ማዕከልን ባስጎበኙበት ወቅት የህዝባችንን እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ሆነ የሀገራችንን እድገት ለማፋጠን ሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ስኬታማነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባቸው ጠይቀዋል፡፡
አቶ ጫላ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት መማር የሚጠበቅባቸውን ጎልማሶች ለይቶ በማወቅ አሳምኖ ወደ ስልጠና ማዕከሉ በማምጣትም ሆነ በመማር ማስተማር ሂደቱም ላይ ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ጫላ አክለውም በያዝነው በ2016 ዓ.ም በወረዳው 4,623 ጎልማሶች በ60 የማስተማሪያ ማዕከላት ውስጥ በመማር ላይ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡
የብልብሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ጥበቡ አንበሴ ለጎልማሶች መማሪያ ማዕከሉ ከመደበኛው ትምህርት እኩል ትኩረት ሰጥተው እያስተዳደሩ መሆኑን ጠቁመው ይህ መሆኑ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልጸዋል፡፡
የማዕከሉ አመቻች መምህርት ስኳሬ ድሪባ ለፕሮግራሙ በተዘጋጀው መመሪያ መሰረት የአንድ አመት ትምህርታቸውን በውጤታማነት ያጠናቀቁ ጎልማሶች በመደበኛው ትምህርት 3ኛ ክፍል ገብተው ትምህርታቸውን መቀጠል የሚችሉ መሆኑን ጠቁመው ይህንን መብታቸውን ለመጠቀም ጥቂት የማይባሉ ጎልማሶች ከወዲሁ ከአፋን ኦሮሞ በተጨማሪ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መሰረታዊ ትምህርትም እንዲሰጣቸው መጠየቅ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡
በኦሮሚያ ብ/ክ/መ/በአርሲ ዞን የሌሙና ብልብሎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጫላ አበራ የቢልቢሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የጎልማሶች መማሪያ ማዕከልን ባስጎበኙበት ወቅት የህዝባችንን እኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ሆነ የሀገራችንን እድገት ለማፋጠን ሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም ስኬታማነት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባቸው ጠይቀዋል፡፡
አቶ ጫላ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት መማር የሚጠበቅባቸውን ጎልማሶች ለይቶ በማወቅ አሳምኖ ወደ ስልጠና ማዕከሉ በማምጣትም ሆነ በመማር ማስተማር ሂደቱም ላይ ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ጫላ አክለውም በያዝነው በ2016 ዓ.ም በወረዳው 4,623 ጎልማሶች በ60 የማስተማሪያ ማዕከላት ውስጥ በመማር ላይ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡
የብልብሎ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ጥበቡ አንበሴ ለጎልማሶች መማሪያ ማዕከሉ ከመደበኛው ትምህርት እኩል ትኩረት ሰጥተው እያስተዳደሩ መሆኑን ጠቁመው ይህ መሆኑ ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋጽኦ እንደነበረው ገልጸዋል፡፡
የማዕከሉ አመቻች መምህርት ስኳሬ ድሪባ ለፕሮግራሙ በተዘጋጀው መመሪያ መሰረት የአንድ አመት ትምህርታቸውን በውጤታማነት ያጠናቀቁ ጎልማሶች በመደበኛው ትምህርት 3ኛ ክፍል ገብተው ትምህርታቸውን መቀጠል የሚችሉ መሆኑን ጠቁመው ይህንን መብታቸውን ለመጠቀም ጥቂት የማይባሉ ጎልማሶች ከወዲሁ ከአፋን ኦሮሞ በተጨማሪ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መሰረታዊ ትምህርትም እንዲሰጣቸው መጠየቅ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡
Apr 16, 2024 342
የሀገር ውስጥ ዜና

መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በመደበኛ ት/ቤቶች የትምህርት መጠነ-ማቋረጥን እንዲቀንስ ማድረጉ ተገለጸ

ሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ትምህርት ቢሮ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆኑ ትምህርቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሻለ ሸለመ እንደገለጹት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጠን መቋረጥ ፣ ማርፈድና ከትምህርት ገበታ መቅረት እንዲቀንስ አስችሏል፡፡
እንደ ሃላፊው ገለጻ በትምህርት ቤቶች መጠነ - ማቋረጥ የቀነሰው በክልሉ ሰላሳ ሰባት ወረዳዎች መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶችና ወላጆች የትምህርትን ጠቀሜታ በመገንዘብ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤቶች በመላካቸውና አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ በመጀመራቸው ነው።
በክልሉ መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት የማይችሉ ጎልማሶች ማንበብና መጻፍ እንዲሁም መሰረታዊ የሂሳብ ስሎቶችን ማስላት መቻላቸውንም የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ዳይሬክተሩ አመልክተዋል።
ጎልማሶቹ ከስራቸውና ከእለት ተለት የኑሮ እንቅስቃሴዎቻቸው ጋር የተዛመዱ ትምህርቶችን በመማራቸው በቁጠባ ፣ በማዳበሪያና ምርጥ ዘር አጠቃቀም፣ በኮምፖስት ዝግጅት ፣ በዶሮ እርባታና በሌሎችም በእርሻና እንስሳት ልማት ስራዎቻቸው ውጤታማና ምርታማ መሆናቸውን አቶ ተሻለ ተናግረዋል፡፡
የዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ላሜሶ እና የዳራ ወረዳ ት/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በበኩላቸው በወረዳው የጎልማሶች ትምህርት ማዕከላት መሰረታዊ ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶች ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት ብቻ ሳይሆን በኑሯቸውም ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በ2016 የትምህርት ዘመን በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች 75ሺ 443 ጎልማሶች በ 1ሺህ 320 የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ተመዝግበው በመማር ላይ እንደሚገኙ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ትምህርት ቢሮ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆኑ ትምህርቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሻለ ሸለመ እንደገለጹት በክልሉ ተግባራዊ የተደረገው መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጠን መቋረጥ ፣ ማርፈድና ከትምህርት ገበታ መቅረት እንዲቀንስ አስችሏል፡፡
እንደ ሃላፊው ገለጻ በትምህርት ቤቶች መጠነ - ማቋረጥ የቀነሰው በክልሉ ሰላሳ ሰባት ወረዳዎች መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶችና ወላጆች የትምህርትን ጠቀሜታ በመገንዘብ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤቶች በመላካቸውና አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ በመጀመራቸው ነው።
በክልሉ መሰረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት የማይችሉ ጎልማሶች ማንበብና መጻፍ እንዲሁም መሰረታዊ የሂሳብ ስሎቶችን ማስላት መቻላቸውንም የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ዳይሬክተሩ አመልክተዋል።
ጎልማሶቹ ከስራቸውና ከእለት ተለት የኑሮ እንቅስቃሴዎቻቸው ጋር የተዛመዱ ትምህርቶችን በመማራቸው በቁጠባ ፣ በማዳበሪያና ምርጥ ዘር አጠቃቀም፣ በኮምፖስት ዝግጅት ፣ በዶሮ እርባታና በሌሎችም በእርሻና እንስሳት ልማት ስራዎቻቸው ውጤታማና ምርታማ መሆናቸውን አቶ ተሻለ ተናግረዋል፡፡
የዳራ ኦቲልቾ ወረዳ ትምህርት ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ ላሜሶ እና የዳራ ወረዳ ት/ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ታደሰ በበኩላቸው በወረዳው የጎልማሶች ትምህርት ማዕከላት መሰረታዊ ትምህርት የሚከታተሉ ጎልማሶች ማንበብ ፣ መጻፍና ማስላት ብቻ ሳይሆን በኑሯቸውም ለውጥ እያመጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በ2016 የትምህርት ዘመን በክልሉ ሁሉም ወረዳዎች 75ሺ 443 ጎልማሶች በ 1ሺህ 320 የጎልማሶች ትምህርት ጣቢያዎች ተመዝግበው በመማር ላይ እንደሚገኙ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
Apr 16, 2024 291

ሚኒስትሮቻችን

MINISTER

ክቡር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ትምህርት ሚኒስቴር

STATE MINISTER

ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ

አጠቃላይ ትምህርት

STATE MINISTER

ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የተቋሙ አደረጃጀት

ይህ ዋናው የትምህርት ሚኒስቴር አወቃቀር ሰንጠረዥ ነው

አጠቃላይ ትምህርት

የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የቋንቋና ተጓዳኝ ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የማህበራዊ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የተፈጥሮ ሣይንስ ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የሥራና የተግባር ትምህርቶች የሥርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ቋንቋዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የሒሳብ፣ ሳይንስና ሥነ ጥበብ መምህራን ማበልፀጊያ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የመደበኛ ትምህርት ኘሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ

የአርብቶ አደርና ልዩ ፍላጐት ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት መሠረተ ልማትና አገልግሎቶች ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ

የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የጐልማሶች መሠረታዊ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ

መደበኛ ያልሆነና የሕይወት ዘመን ትምህርት ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ

የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ

የሥርዓተ-ትምህርትና ኘሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ

የመምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ

የምርምርና ስርጸት ዴስክ ኃላፊ

የምርምር ስነ-ምግባር ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ

የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ

የአስተዳደር እና መሰረተ-ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ

የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ

የተቋማት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የመሠረተ ልማትና ግብዓት ዴስክ ኃላፊ

የስኮላርሽፕና አለማቀፋዊነት ዴስክ ኃላፊ

አይቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ሥራ አስፈፃሚ

የስኩልኔት አይሲቲ ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት የመልቲ ሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ

የትምህርት ሚዲያሰተትዱዮ ኦፕሬሽንና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ

የኔትዎርክ ቴክኒካል ዴስክ ኃላፊ

ኔተዎርክ ኦፕሬሽን ዴስክ ኃላፊ